አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የቀጥታ ሽያጭ ኢንዱስትሪ ላይ የምርምር ማረጋገጫ አውደ ጥናት ሪፖርት ለብሬክስሩ ትሬዲንግ አ.ማ አቅርቧል።
(መጋቢት 5/ 2016ዓ.ም)
በሪፖርቱም ላይ የቀጥተኛ ሽያች ኢንዱስትሪ በማህበራዊ እና እና በኢኮኖሚ ላይ የሚያመጣውን ተጽዕኖ እንደዚሁም ከህግ አንጻር የምርምር ማረጋገጫ አውደ ጥናት ቀርቧል።
የለውጥ ትውልድ ስልጠናዎች በዳውሮ ዞን!
የለውጥ ትውልድ ስልጠናዎች በዳውሮ ዞን ደ/ም/ኢ/ክ... በ ቶጫ እና ገሳ ጫሬ አካባቢ ወረዳዎች ተሰጥቷል!
በፍቅራችን፣ በግልጽነታችን፣ በአገልጋይነታችን፣ በትጉህ ስራችን፣ እና በቅንነታችን፤ የጋራ ራዕያችን የሆነውን ባለ ራዕይ፣ ቅን፣ ጤናማ እና ባለፀጋ ትውልድን መፍጠር፣ ከግብ ለማድረስ ጉዞአችንን እንቀጥላለን።
በማገልገል እና በመስጠት፤ ትክክለኛ የሆነውን የህይወት ጣዕምን እናገኛለን።
ቶጫ ኮምዩኒኬሽን በፌስቡክ ገጻቸው ላይ ብሬክስሩ ትሬዲንግ አ.ማ በማስተባበር በአወንታዊ አስተሳሰብ ግንባታ፣ በራዕይ ቀረጻ እና በገቢ ማስገኛ ዙሪያ ለወጣቱ ስልጠና ያሰጡትን ተወካዮችን እና ድርጅታች ብሬክስሩን የወረዳው ም/ል አስ/ሪ ኮማንደር አድነው ወርቁ አመስግኗል። ሙሉ ዘገባውን ከታች ባለው ሊንክ ይከታተሉ
https://www.facebook.com/share/p/7DhxGpM1V8sM93hn/?mibextid=oFDknk
Source: Tocha Communication
ብሬክስሩ ትሬዲንግ አ.ማ ከሴቶች እና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር ጋር የ8 ዓመት ፕሮጀክት የስምምነት ፊርማ ተፈራርሟል።
በዚህ የ8 ዓመት ፕሮጀክት ላይ የለውጥ ትውልድ በሚል የፕሮጀክት ስያሜ፤ ወደ 20,000,000 የሚጠጉ ወጣቶችን ነጻ የግል ስብዕና ማጎልበቻ ስልጠና ለመስጠት ከሴቶች እና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር ጋር የጋራ ስምምነት ላይ ተደርሷል።
ይህንንም ፕሮጀክት ለመጀመር የመግባቢያ ስምምነት በቀን የካቲት 19/ 2016ዓ.ም፤ ብሬክስሩ ትሬዲንግ አ.ማ ከሴቶች እና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር ጋር ተፈራርሟል።
ትምህርታዊ ስልጠናዎችን በመሸጥ 206 ሚሊዮን ብር ማግኘት መቻሉን ብሬክስሩ አሳዉቋል!
(ካፒታል : ጥር 15፤2016 ዓ.ም.)
በኢትዮጵያ በግል ስብእና ላይ ያተኮሩ ስልጠናዎችን እየሰጠ ላለፉት 4 ዓመታት መቆየቱን የሚገልፀዉ ብሬክስሩ ትሬዲንግ አክስዮን ማህበር በተለያዩ ትምህርታዊ ፓኬጆችን በመሸጥ በተጠናቀቀዉ ዓመት 206 ሚሊዮን ብር ማግኘቱን ገልጿል።
የሼር እና ኔትወርክ ማርኬቲንግ ካምፓኒ ሆኖ በ17 ሰዎች የተመሰረተው ብሬክስሩ ከ 41 ሺህ በላይ አባላቶችን በመያዝ የስብዕና ግንባታን እየሰጠ እንደሚገኝ ገልጿል።
የድርጅቱ ዋና ስራ አስኪያጅ አብድል ፈታ "ሰዎች ዝንባሌያቸውን እና ህልማቸውን እንዲያዉቁ በሳይንሳዊ መልኩ ስልጠናዎች እንሰጣለን ይህንን ለመዉሰድ ክፍያ ይፈፅማሉ" በማለት ተናግረዋል።
ቅን እና ባለዕራይ ሰዎችን መፍጠር ዓላማው እንደሆነ የገለፀዉ ካምፒኒዉ በስልጠናው ሰዎች ህልማቸውን እንዲያዉቁ ከተደረገ በኃላ በተለያዩ መልኩ ስልጠናዎችን በመስጠት እራሳቸውን እንዲፈልጉና የግላቸውን ቢዝነስ እንዲጀምሩ እንዲሁም ከብሬክስሩ ጋር አብረዉ እንዲሰሩ አማራጭ እንሰጣለን በማለት አስረድተዋል ።
ስልጠናውን ከወሰዱ ከ41 ሺህ በላይ ሰዎች መካከል ከ 10 ሺህ በላይ የሚሆኑት የራሳቸውን የገቢ ምንጭ ፈጥረዉ በቋሚነት እየሰሩ እንደሚገኙ አብድል ፈታ ሁሴን ተናግረዋል።
ብሬክስሩ ትሬዲንግ አክስዮን ማህበር በዚህ ዓመት ለስልጠና ከሚያቀርባቸው ፓኬጆች በዚህ ዓመት 1 ቢሊዮን ብር ለማግኘት እቅድ እንዳለዉ አሳዉቆ ከኢትዮጵያ በተጨማሪ ከኢትዮጵያ በተጨማሪ በኬንያ ፣ በደቡብ አፍሪካ ፣ በደቡብ ሱዳን ፣ እስራኤል እና ስዊድን ቅርንጫፎች መክፈቱን እንዲሁም ስልጠናዎችን እየሰጠ እንደሚገኝ ለማወቅ ተችሏል ።
"የኔ" የተሰኘ የሙያ ብቃት የሚጨምር የኦንላይን አጋር የሙያ መሳሪያ ምርት በድርጅታችን ብሬክስሩ ይፋ ተደረገ።
“የኔ” ምርት በአለምአቀፍ ደረጃ እና በሀገር ውስጥ ባሉ ኩባንያዎች ውስጥ በከፍተኛ እና በስነ-ልቦና ጥናታዊ የተደገፈ ሲሆን፤ የቅጥር ብቃትን የሚጨምር መሳሪያ ነው። “የኔ” ከዘጠነኛ ክፍል ጀምሮ ላሉ ተማሪዎች እና ለማንኛውም ሰው የሚሆን ሲሆን፤ በስነ-ልቦና የተረጋገጠ ምርት እንደዚሁም በሆላንድ ኮድ እና 250 የመረጃ ነጥቦችን በመጠቀም አንድ ሰው ምን አይነት ስብዕና እንዳለው ለመለየት እና የትኛውን የሙያ መስመር መከተል እንዳለበት ለማወቅ የሚረዳ ነው።
የድርጅታችን የቦርድ ሰብሳቢ የሆኑት አቶ ነፃነት ዘነበ(ኢፕኖቴራፒስት) ባደረጉት ንግግር "በደቡብ አፍሪካ 150ሺ ወጣቶች ተጠቃሚ የሆኑበት ይህ ምርት አሁን በኢትዮጵያ ወጣቶች እስከ 4ሺ የክህሎት ስልጠናዎችን በመውሰድ በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ እንዲሆኑ የሚያስችል የመፍትሄ አካል ነው ይዘን የመጣነው" ብለዋል።
"የኔ" ሰዎች ማንነታቸውን አውቀው ከማንነታቸው ጋር የሚሄድ የትምህርት ዘርፍ እንዲመርጡ የሚረዳቸው ሲሆን በዚህም ምክንያት በተፈጥሮ ያላቸው ዝንባሌ እና ጥንካሬ ላይ ተመርከዘው የትምሀርትም ሆነ የስራ ዘርፋቸውን ስለሚመርጡ ደስተኛ እና ውጤታማ ሆነው እንዲማሩ ብሎም ህይወታቸው ላይ ተፅዕኖ ፈጣሪ እና ውጤታማ እንዲሆኑ ታላቅ አስትዋፅዖ የሚያደርግ ምርት ነው። በተጨማሪም ተማሪዎች ስኮላርሺፖችን እንዲያገኙ የተለያዩ የኮሌጆችን እና ዩኒቨርሲዎችን መረጃዎች በየኔ ኦንላይን መድረክ ላይ በማግኘት አለምአቀፋዊ ዕድሎችን ተማሪዎች እንዲያገኙ ያግዛል።
"የኔ" ምርት ከየንዛ (Yenza) እና ከደቡብ አፍሪካ ስታንዳርድ ባንክ (Standard Bank) ጋር በመተባበር የበለፀገ አለምአቀፍ የኦንላይን የሙያ መሳሪያ ምርት ነው።